ከጥቂት ወራት ወዲህ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረ ከሳቡ ወሳኝ ጉዳዮች ውስጥ የዐማራ
መደራጀት ዋናው ሳይሆን አልቀረም። ይህን ጉዳይ በተመለከተ በርካታ ጽሑፎችና ንግግሮች ተደርገዋል። ዐማራው እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነገድ መደራጀትና ራሱን ከተቀነባበረ ጥፋት
ማዳን እንዳለበት የሚሞግቱ በርካቶች ናቸው። አሳማኝ የመከራከሪያ ነጥቦችንም አንስተዋል። በአንጻሩ ደግሞ ዐማራው በኢትዮጵያዊነት እንጅ በነገዱ መታገል መዘዙ ብዙ እንደሆነ ያስጠነቀቁ አሉ። ከሁለቱም ወገኖች አንዳንዶች ነጥቦቻቸውን በምክንያት ወይም በመረጃና በማስረጃ
መደገፍ ሲሳናቸው አፍ አውጥተው ሌሎች ጸሐፍትን ሲሳደቡና «ወያኔ ነህ» «ጸረ ዐማራ ነህ» እያሉ ሲያሸማቅቁ ታይተዋል። ከነዚህ ከተሳዳቢዎችና ከአሸማቃቂዎች በስተቀር ለሌሎች ጸሐፍት ከፍ ያለ አክብሮትና
ምሥጋና አቀርባለሁ። መሠረት ያላቸው ውይይቶችና ክርክሮች ለሚደረገው ትግል ግልጽነትንና መናበብን ይፈጥራሉና!
Thursday 8 December 2016
Saturday 26 November 2016
Asrat Woldeyes & Ethiopian Politics
September 1997. I was in Bichena, the stronghold of the hero Belay Zeleke. My plan
was to reach at Addis Ababa University (AAU) for registration as a final year
undergraduate student. Unfortunately, the scheduled bus failed to appear. Everyday
around 6pm, we passengers were supposed to get registered afresh, hoping the bus
could come the next day. We did registration six times, that is for six days. My
money generously given by my relatives run real fast and I was in shock. But most
worrisome was whether I could reach for the registration at AAU. Every passing day
seriously touched my nerves. That time, no mobile, no Internet. It was real dark time.
undergraduate student. Unfortunately, the scheduled bus failed to appear. Everyday
around 6pm, we passengers were supposed to get registered afresh, hoping the bus
could come the next day. We did registration six times, that is for six days. My
money generously given by my relatives run real fast and I was in shock. But most
worrisome was whether I could reach for the registration at AAU. Every passing day
seriously touched my nerves. That time, no mobile, no Internet. It was real dark time.
Saturday 8 October 2016
የወቅቱ ፖለቲካዊ አሰላለፍና ፋይዳው
የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል እየሰፋና ቀጣይነቱን እያረጋገጠ ሲሄድ በውጭው ዓለም የሚገኙ
ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ባህርያቸውን ይበልጥ እየገለጡ መጥተዋል። ግለሰብ ተኮር እንቅስቃሴዎች ወደ ድርጅት ወይም ማኀበር ወይም ኅብረት እየተለወጡ
ነው። ይበልጥ ትኩረት እየሳበ
የመጣው ግን የድርጅቶቹ ብዛት ሳይሆን የተነሱበት ዓላማ ወይም ግብ ነው። የአንዳንዶች የትግል ባህርይ ከተጠበቀው በአንፃሩ ሆኖ በመገኘቱ ጥቂት በማይባሉ
ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ቁጣና ግርምትን ፈጥሯል። ይህን ተከትሎ ክርክሮችና ተግሳጾች በመገናኛ ብዙኃን እየወጡ ነው። እኒህ አይነት እንቅስቃሴዎች ትግሉ ምን ያህል ሰላማዊና አንድነትን የተላበሰ እንደሚሆን
ካሁኑ ግርታን ፈጥረዋል።
Friday 9 September 2016
ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ!
በአገራችን በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ እጅግ አሳዛኝ፣ አሳሳቢ፣ አጓጊም ሆኗል። ፈጣሪ በኋላም ዓለም አቀፍና ብሄራዊ ሕግጋት የሰጧቸውን በፍጹም በነጻነት የመኖር መብታቸው እንዲከበርላቸው የጠየቁ ወገኖቻችን በመሰዋታቸው፣ አካለ ስንኩላን በመሆናቸው፣ የሲዖል አምሳያ በሆኑ እስር ቤቶች በመጋዛቸው፣ መከራ ለበዛበት ስደት በመዳረጋቸው፣ ባጠቃላይ እንደ ሰው በሰላም መኖር ባለመቻላቸው ሃዘናችን ወሰን የለውም። በአንጻሩ ደግሞ ለመኖር እየተደረገ ያለው አለመኖር ማለትም ትግል መንግስትን ክፉኛ ስላሸበረውና ደካማነቱን ከምንም ጊዜ በላይ አጉልቶ በማሳየቱ ሁኔታውን አጓጊ አድርጎታል። ምንም ይሁን ምን ካሁን በኋላ መንግስትም ሕዝብም በነበሩበት የመግዛትና የመገዛት ሂደት ውስጥ መቀጠል አይችሉም። ይህም አንዳች ለውጥ ሊመጣ እንዳለው አመላካች ስለሆነ ትግሉ ውጤታማ እየሆነ እንደመጣ ይገነዘቧል።
Friday 19 August 2016
ድር ቢያብር አንበሳ ያስር!
ታሪካዊ የለውጥ ጎዳና ለኢትዮጵያ
በሚል ርዕስ በአገራችን እየተደረገ ያለው የሕዝብ ተቃውሞ አስፈላጊና አበረታች እንደሆነ ሞግቻለሁ። የትግሉም ዓላማ እውነተኛና ዘላቂ ዴሞክራሲና ነጻነት ማስፈን እንደሆነም ከሕዝቡ መፈክሮች በመነሳት አትቻለሁ። በተጨማሪም መንግስትና ደጋፊዎቹ፣ ትግሉን በማካሄድ
ላይ ያለው ሰፊው ሕዝብ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት ተቋማትና የመገናኛ ብዙኅን ይህን መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት ልዩና ላቅ
ያለ አስተዋጽዖ ማድረግ እንዳለባቸው ጠቁሜያለሁ። ሕዝቡ የትግሉ ባለቤትና ኦዲተር ሆኖ ሥራ አሥፈጻሚ
አካል ወይም ልዩ ብሄራዊ ኮሚቴ መምረጥ እንዳለበትም ለማሳየት ሞክሬ ነበር። በመጨረሻም ኮሚቴው ለምንና
እንዴት መመረጥ እንዳለበት ለመነሻ ያህል ጥቂት ነጥቦችን አንስቻለሁ። በዚህ ጽሑፍ ደግሞ ይህ ለውጥ አስተባባሪ ኮሚቴ እንዴት እንደሚመረጥና
የትግል መርሆቹና ስልቶቹ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ዘርዘር አድርጌ አቀርባለሁ።
Wednesday 10 August 2016
ታሪካዊ የለውጥ ጎዳና ለኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊያን እጅግ
የተቀናጀ፣ ያመረረና ቀጣይነትም ያለው የሚመስል ተቃውሞ በመንግስት ላይ እያካሄዱ ይገኛሉ። ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሏል። የአዲስ አበባ የመስፋፋት እቅድና
የመሬት ቅርምት እና የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ቢያነሳሱትም መሠረታዊ የሆኑ የመብትና የነጻነት እንዲሁም የፍትህ
ጥያቄዎች እየተነሱ ነው። ትግሉ በሰላማዊ ሰልፍ ተጀምሮ ሁለ ገብ የሆኑ ስልቶችን ወደ መጠቀም የተሸጋገረ ይመስላል። በመቶዎች የሚቆጠሩት
ሰልፈኞች በመንግስት ታጣቂዎች ተገለዋል፣ ቆስለዋል፣ ታስረዋል። ከመንግስት በኩልም ቁጥራቸው ያልታወቀ ወገኖች ሞተዋል፣ ቆስለዋል። የታሰሩ ግን የሉም።
ይህም ሁሉ መከራ ወርዶ ህዝቡ ለበለጠ ትግል ተነሳስቷል። እስካሁን የተከናወኑት ክስተቶች እንዲሁም ህዝቡ የሚያስተጋባቸው መፈክሮች
በግልጽ እንደሚያሳዩት መንግስት በከፍተኛ ሁኔታ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነትን
እንዳጣ ለመረዳት ችሏል። ለመሆኑ ህዝባዊ ትግሉ አስፈላጊ ነውን?
Thursday 30 June 2016
ማኅበረ ቅዱሳንና ፈታኞቹ የመጨረሻው ክፍል
መግቢያ
ስለወቅታዊ ጉዳዮች ለመጻፍ ተነሳስቼ ነበር። ዳሩ ግን ከዚህ በፊት ስለማኅበረ
ቅዱሳን ሁለት ተከታታይ ጽሑፎችን አቅርቤ ሦስተኛውን እንደምቀጥልበት ቃል መግባቴ ትዝ አለኝ። ጥቂት አንባቢዎቼም «እስካሁን የጻፍካቸው ሁለቱ ጽሑፎች መግቢያ ናቸው። ዋናውን አስከትልና እንተያያለን!» ብለውኝ እንደነበርም ትዝ አለኝ። እናም በሥራ ምክንያት አቋርጨው የነበረውን የጀመርኩትን ጨርሼ እጅግ ወቅታዊ ወደሆኑ ጉዳዮች ማተኮር እንዳለብኝ ወስኜ
ይህን የመጨረሻውን ክፍል አቀረብኩ። በዚህ አጋጣሚ አስተያየት የሰጣችሁኝን ሁሉ ከልብ እያመሰገንኩ ወደ ክፍል 3 ላምራ!
Saturday 16 April 2016
ማኅበረ ቅዱሳንና አራቱ ፈታኞች ክፍል 2
በክፍል 1 ጽሑፌ ስለማኅበረ ቅዱሳን (ማቅ)
መጻፍ ለምን እንዳስፈለገ፣ ማኅበሩን እንዴት እንዳወቅኩትና ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ የማኅበሩን አመሰራረትና ዓላማ
በጥቂቱ አቅርቤያለሁ። በዚህ ክፍል ደግሞ ማቅን አብዝተው የሚፈትኑ አካላት እነማን እንደሆኑ በደረጃ ከነምክንያቶቻቸው
አቀርባለሁ። ይህ ጽሑፍ በክፍል 1 እንደተጠቀሰው ማቅንም ሆነ ሌላ አካልን ለመቃወምም ሆነ ለመደገፍ
የተዘጋጀ አይደለም። ያሉ እውነታዎችን ከግል እይታዬ በመነሳት በትንተና መልክ ለአንባቢ ማስገንዘብ እንጅ። በዚህ ጽሑፍ ምክንያት ሊነሱ የሚችሉ ውይይቶችና
ሙግቶች በመጨረሻ የተሻለ ግንዛቤ እንዲመጣ ያደርጋሉ ብዬ አምናለሁ። ለጽሑፎቼ እንደ ግብዓት ያገለገሉኝ የግል ተሞክሮዬ፣ የማቅ ገጸ ድርና እትሞች እንዲሁም ስለማቅ
በተለያዩ ሚዲያዎች የተነሱ ዘገባዎች ናቸው።
በክፍል 1 ጽሑፌ ስለማኅበረ ቅዱሳን (ማቅ)
መጻፍ ለምን እንዳስፈለገ፣ ማኅበሩን እንዴት እንዳወቅኩትና ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ የማኅበሩን አመሰራረትና ዓላማ
በጥቂቱ አቅርቤያለሁ። በዚህ ክፍል ደግሞ ማቅን አብዝተው የሚፈትኑ አካላት እነማን እንደሆኑ በደረጃ ከነምክንያቶቻቸው
አቀርባለሁ። ይህ ጽሑፍ በክፍል 1 እንደተጠቀሰው ማቅንም ሆነ ሌላ አካልን ለመቃወምም ሆነ ለመደገፍ
የተዘጋጀ አይደለም። ያሉ እውነታዎችን ከግል እይታዬ በመነሳት በትንተና መልክ ለአንባቢ ማስገንዘብ እንጅ። በዚህ ጽሑፍ ምክንያት ሊነሱ የሚችሉ ውይይቶችና
ሙግቶች በመጨረሻ የተሻለ ግንዛቤ እንዲመጣ ያደርጋሉ ብዬ አምናለሁ። ለጽሑፎቼ እንደ ግብዓት ያገለገሉኝ የግል ተሞክሮዬ፣ የማቅ ገጸ ድርና እትሞች እንዲሁም ስለማቅ
በተለያዩ ሚዲያዎች የተነሱ ዘገባዎች ናቸው።
Friday 8 April 2016
ማኅበረ ቅዱሳንና አራቱ ፈታኞች
ማኅበረ ቅዱሳንን በሚገባ ያወቅሁት የዛሬ 20 ዓመት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ግቢ የመጀመሪያ ድግሪ ተማሪ እያለሁ ነው። ማኅበሩ ገና በእግሩ ለመቆም ጥረት በሚያደርግበት ወቅት ። ማኅበረ ቅዱሳን (ከዚህ በኋላ ለማሳጠር ያህል ማቅ ወይም ማኅበሩ እያልኩ እጽፋለሁ) ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ በዩኒቨርስቲው ዋና ግቢ ያሉትን ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ በሚገኘው ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ባቋቋሙት ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ጋበዘ ። ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀምሮ በሰንበት ትምህርት ቤት ተሳታፊ ስለነበርኩና የዕውቀትም ጥማት ስለነበረብኝ የማኅበሩን ግብዣ በታላቅ ደስታ ተቀበልኩት።
Friday 5 February 2016
ስደት ክርስትናና ኢትዮጵያዊነት ክፍል 2
ለተገፉት መቆም
ክርስትና በግል የሚኖሩት ሕይወት አይደለም:: «እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት ለባልንጀራው እንጅ»
(ፊል 2: 4) እንዳለ ለሰው ልጅ ሁሉ ይልቁንስ ለኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ደኅንነት ማሰብና የምንችለውን
ማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችን ነው:: በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በአፍሪካና በአውሮፓም ሳይቀር
ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በመከራ ላይ ናቸው:: የሰው ልጅ የገጠመው ከባድ የተባለ መከራ ሁሉ የደረሰባቸው
አሉ:: በየእስር ቤቶች የሚጉላሉና ጠያቂ ያጡ ብዙዎች ናቸው:: በደላሎችና በአሸባሪዎች እጅ የወደቁት ብዙ ናቸው:: የሰውነት ክፍሎቻቸው ለሽያጭ የቀረቡባቸው አሉ:: በሃይማኖታቸው ምክንያት መስዋዕትነትን የተቀበሉም አሉ:: ባጠቃላይ በሞትና በህይወት መካከል የሚገኙ ወገኖቻችን ብዙዎች ናቸው:: በአገራችን በኢትዮጵያም ቢሆን ያለአግባብ በእስር የሚማቅቁ፣ የሚገደሉ፣ የሚሳደዱ አሉ:: በረሃብ የሚሰቃየው ወገናችንም በሚሊዮን የሚቆጠር ሆኗል:: ሙስናና ዘረኝነት ህዝባችንን ተፈታትኗል:: ለእነዚህ ሁሉ ወገኖች ኢትዮጵያዊያን ሊደርሱላቸው ይገባል:: በጸሎት ከማሳሰብ ጀምሮ ገንዘብና አስፈላጊ ቁሳቁስ በመላክ እንታደጋቸው::
Friday 29 January 2016
ስደት ክርስትናና ኢትዮጵያዊነት
ስደት ለምን?
ስደት ከትውልድ አገር በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ወጥቶ በሌላ አገር ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ መኖርን ያመለክታል:: በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ስደተኞች አዳምና ሔዋን ናቸው:: ምንም እንኳን እግዚአብሔር ከምድር አፈር ቢፈጥራቸውም አገራቸው በምሥራቅ በኩል ባለች በኤዶም ገነት ይሆን ዘንድ ፈቃዱ ሆነ:: አዳም በተፈጠረ በ40 ቀኑ ሔዋን በተፈጠረች በ80 ቀኗ ኤዶም ገነት ገቡ:: በዚያም ሰባት ዓመት ከአንድ ወር ከ17 ቀን በደስታ ከኖሩ በኋላ ጠላት ዲያብሎስ በእባብ ተመስሎ አሳታቸው:: የታዛዥነት ምልክት የሆነችውን ያልተፈቀደላቸውን ዕፀ በለስን ስለበሉ እግዚአብሔር ከገነት አስወጣቸው:: በተፈጠሩባት ምድር በድካም እንዲኖሩ ተፈረደባቸው:: ስደት ወደ ምድር:: አዳምና ሔዋን እግዚአብሔርን በማሳዘናቸውና ገነትን በማጣታቸው ሐዘን ላይ እያሉ ክፉ ልብ የነበረው (1ዮሐ 3: 11 - 12) ልጃቸው ቃየን በቅናት ተነሳስቶ ወንድሙን አቤልን ገደለው:: በእግዚአብሔር አምሳያ የተፈጠረውን ሰውን በመግደል የመጀመሪያው ሰው ሆነ:: ከቤተሰቡና ከእግዚአብሔር ቁጣ የሚያመልጥ መስሎት ኖድ ወደተባለ አገር ተሰደደ:: እድሜ ልኩን ተቅበዝባዥ ሆነ:: ባጠቃላይ ሲታይ የዚህ ቤተሰብ አባላት ማለትም አዳም ሔዋንና ቃየን መራር ለሆነ ስደትና መከራ የተዳረጉት በራሳቸው ኃጢአት የተነሳ ነው::
Subscribe to:
Posts (Atom)
Who will Win: Fano or the Government?
The government's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more complicated than everyone’s expectation. ...