Friday 5 February 2016

ስደት ክርስትናና ኢትዮጵያዊነት ክፍል 2

ለተገፉት መቆም  

ክርስትና በግል የሚኖሩት ሕይወት አይደለም:: «እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት ለባልንጀራው እንጅ»  (ፊል 2: 4) እንዳለ ለሰው ልጅ ሁሉ ይልቁንስ ለኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ደኅንነት ማሰብና የምንችለውን ማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችን ነው:: በመካከለኛው ምሥራቅ በአፍሪካና በአውሮፓም ሳይቀር ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በመከራ ላይ ናቸው:: የሰው ልጅ የገጠመው ከባድ የተባለ መከራ ሁሉ የደረሰባቸው አሉ:: በየእስር ቤቶች የሚጉላሉና ጠያቂ ያጡ ብዙዎች ናቸው:: በደላሎችና በአሸባሪዎች እጅ የወደቁት ብዙ ናቸው:: የሰውነት ክፍሎቻቸው ለሽያጭ የቀረቡባቸው አሉ:: በሃይማኖታቸው ምክንያት መስዋዕትነትን የተቀበሉም አሉ:: ባጠቃላይ በሞትና በህይወት መካከል የሚገኙ ወገኖቻችን ብዙዎች ናቸው:: በአገራችን በኢትዮጵያም ቢሆን ያለአግባብ በእስር የሚማቅቁ የሚገደሉ የሚሳደዱ አሉ:: በረሃብ የሚሰቃየው ወገናችንም በሚሊዮን የሚቆጠር ሆኗል:: ሙስናና ዘረኝነት ህዝባችንን ተፈታትኗል:: ለእነዚህ ሁሉ ወገኖች ኢትዮጵያዊያን ሊደርሱላቸው ይገባል:: በጸሎት ከማሳሰብ ጀምሮ ገንዘብና አስፈላጊ ቁሳቁስ በመላክ እንታደጋቸው::

Who will Win: Fano or the Government?

  The government's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more   complicated than everyone’s expectation. ...