Saturday, 11 February 2023
የመንግስትና የቤተ ክርስቲያን ስምምነት እንዴት?
ጥር 14 ቀን 2015 ዓ/ም የተካሄደው ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሲመት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለመንግስትና ለሀገራችን ኢትዮጵያም ከፍተኛ ውጥረትን አስከትሏል። ቤተ ክርስቲያንም ሿሚዎችንም ተሿሚዎችንም አውግዛ ለየቻቸው። መንግስትም በበኩሉ ሕግ የማስከበር ሥራውን እንዲወጣ ቤተ ክርስቲያን አሳሰበች። ይሁንና መንግስት ለሕገ ወጡ ቡድን ሀሳብና ሞራል በመስጠት እንዲሁም ታጣቂዎችን በማሰማራት ሕገ ወጡ ቡድን አብያተ ክርስቲያናትንና መንበረ ጵጵስናዎችን በኃይል እንዲቆጣጠር ማገዙን ቀጠለ። በመሆኑም ጉዳዩ በዋናነት በመንግስትና በቤተ ክርስቲያን መካከል ሆነ። መንግስት ሕግ የማስከበር ግዴታውን እንዲወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ ላለፉት ሦስት ሳምንታት ሲወተውት ቆይቷል። የካቲት ሦስት ቀን 2015 ዓ/ም መንግስትና ሲኖዶሱ ለሦስት ሰዓታት የፈጀ ስብሰባ በቤተ መንግስት አካሂደዋል። ይህን ተከትሎ ዛሬ የካቲት አራት ቀን 2015 ዓ/ም ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን አቋም ሙሉ በሙሉ ተቀብሏል።
Subscribe to:
Comments (Atom)
Just War and the Fano Struggle: A Brief Moral Evaluation
Moral judgments about war are among the most consequential determinations scholars and societies make. They shape legitimacy, responsibilit...