Wednesday, 6 August 2014

ሰላማዊ ሕዝባዊ ትግል!


ሰላማዊ ትግልን አልፎ  አልፎ  በሚደረግ ሰላማዊ ሰልፍና በየአምስት ዓመቱ በሚመጣ ምርጫ መሳተፍ የምንወስነው ከሆነ ይህ የትግል ስልት ውጤት የለውም:: ዳሩ ግን በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች እንደሚነግሩን ሰላማዊ ትግል እጅግ ሰፊ ግን ተደጋጋፊ ስልቶችን ያካትታል:: ይህ ከግምት ውስጥ ሲገባ ወደ አንድ ድምዳሜ ይወስደናል:: ሰላማዊ ህዝባዊ ትግል በኢትዮጵያ አንዱዓለም አራጌ እንደገለጸው ገና ያልተሄደበት መንገድ ነው:: እስካሁን ፖለቲካዊ ለውጥ ያልመጣው አማራጭ የሰላማዊ ትግል ስልቶች ተቀነባብረውና በቀጣይነት ሥራ ላይ ስላልዋሉ ነው::

Saturday, 12 July 2014

አገራዊ ስሜት ለምን ይጎድለናል? የመጨረሻ ክፍል

አብዛኛው ኢትዮጵያዊ አገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ቀዝቃዛ ስሜት እንዳለውና በቂ ተሳትፎ እንደማያደርግ በመደምደም የችግሩን መንስኤዎች ወይም ምክንያቶች በተከታታይ ጽሁፎች ማቅረብ ጀምሬአለሁ:: ክፍል አንድ አገራዊ ስሚት ምን ማለት እንደሆነ ካብራራ በኋላ ብዙው ኢትዮጵያዊ በብሄራዊ ጉዳዮች የመሳተፍ ዝንባሌና ፍላጎት እንዲሁም ሥነ-ልቡናዊ አቅም እንደሌለው አትቷል:: ክፍል ሁለት ደግሞ ባህላዊ አስተምህሮቶቻችን ፖለቲካዊ አገራዊ ጉዳዮችን በንቃት እንዳንከታተል ተጽዕኖ እንዳደረጉብን አብራርቷል:: እንዲሁም ብዙ ሰዎች ተሳትፎ ቢያደርጉ መንግስት በህይወታቸው: በቤተሰባቸውና በሥራቸው ላይ መከራ እንደሚያመጣባቸው በማመን "ዝምታ ወርቅ ነው"ን እያዜሙ እንደሚኖሩ አትቷል:: በዚህ የመጨረሻ ክፍል ደግሞ  ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ጉዳዮች የበኩላችንን አስተዋጽዖ እንዳናደርግ ያደረጉንን ሌሎች እንቅፋቶች ለመዘርዘር እሞክራለሁ:: 

Saturday, 7 June 2014

አገራዊ ስሜት ለምን ይጎድለናል? ክፍል 2

በክፍል አንድ ጽሁፌ ብዙ ኢትዮጵያዊ በቂ የአገር ስሜት እንደሌለው ሞግቻለሁ:: አገራዊ ስሜት ማለትም አገራችንን በተመለከተ የሚነሱ ጉዳዮችን በነቃ አእምሮ ተከታትሎና መርምሮ የራስን ግንዛቤ መውሰድ ከዚያም የሚገባውን አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሆነም ጠቁሜአለሁ:: በስብሰባዎችና የውይይት መድረኮች መሳተፍ: የፖለቲካ ወይም የሲቪል ተቋማትን መምራት ወይም አባል መሆን: የራሱና የሌላ ሰው መብት ሲጣስ መቃወም: እድገትና ለውጥ በሚያመጡ ፕሮጄክቶች መሳተፍ ወዘተ የአገራዊ ፖለቲካዊ ስሜት የሚገለጥባቸው መንገዶች እንደሆኑም ለምሳሌነት አንስቻለሁ:: ከዚያም አገራዊ ጉዳዮችን በአንክሮ እንዳንከታተልና በሚገባ እንዳንሳተፍ የሚያደርጉ መንስኤዎችንና ምክንያቶችን በዝርዝር ማንሳትና መወያየት ፖለቲካዊ ንቃተ ኅሊናን ለማሳደግ በሚደረግ ጥረት አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ አሳስቤአለሁ:: በዚህ ጽሁፍ ሁለት ለአገራዊ ስሜት በበቂ ሁኔታ አለመኖር ተጠቃሽ መንስኤዎችን ወይም ምክንያቶችን ለውይይት አቅርቤአለሁ::   

Friday, 6 June 2014

D-Day: The Ethiopian Type!

Today, June 6, marks the 70th anniversary of the D-Day. Celebrations and commemorations are underway at  Normandy, France. In October 2013, I wrote a piece on Ethiopian politics, see below, by taking into consideration the concept of the D-Day. It was read by 4, 000 people from North America to Europe to Africa including Ethiopia.  I feel the points raised are still relevant and significant to all who gets involved in Ethiopian politics. Have a good read! 

Friday, 30 May 2014

አገራዊ ስሜት ለምን ይጎድለናል

ከበርካታ ሳምንታት በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኢትዮጵያ ስላለችበት ወቅታዊ ሁኔታ እየተወያየን ነበር:: ሁሉም ተሳታፊ የተስማማበት ጉዳይ ቢኖር ኢትዮጵያ ከምንም ጊዜ በላይ እጅግ ከባድ ማኅበራዊ ምጣኔ ሃብታዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ነበር:: ለዚህም በግንባር ቀደምነት ተጠያቂው መንግስት እንደሆነ ቢሰመርበትም ህዝቡም ላለንበት ሁኔታ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ታላቅ አስተዋጽዖ እያደረገ እንደሚገኝ ተወስቷል::

Friday, 14 March 2014

ብአዴንንም ጠበቅ!

              
ኢሕአዴግን እንደመሰረቱ ከሚነገረው አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ኢትዮጵያን በአንደኛ ደረጃ የጎዳ ወይም ያዳከመ የትኛው ነው ብለው ያስባሉ? ለምን? ለዚህ ጥያቄ ወጥ የሆነ መልስ ሊኖር አይችል ይሆናል:: እያንዳንዳችን ያለን አስተሳሰብና ፍልስፍና ሊለያይ ይችላልና:: ነገር ግን በመረጃ ተኮር የአስተሳሰብ ብሂል የሚጓዝ ማንኛውም ሰው ሊሰጠው የሚችለው መልስ ሊመሳሰል ይችላል:: ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ ያለውን የአገራችንን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ መክተት ለምንሰጠው መልስ ጥሩ መነሻ ይሆናል::

Sunday, 5 January 2014

ጎጂ ባህሎቻችን (የመጨረሻው ክፍል)

በዚህ የመጨረሻ ክፍል ከአስተሳሰባችንና ከአመለካከታችን ጋር ቀጥታዊ ግንኙነት አለው ብዬ የማስበውን ጎጂ ባህል አቀርባለሁ:: ይህን ጎጂ ባህል በሚገባ መመርመርና ማስወገድ ከቻልን አገራችን ኢትዮጵያ ከምትገኝበት ሁለንታዊ ችግሮችና ቀውሶች ለመላቀቅ የሚያስችላትን ትክክለኛ መንገድ ልትይዝ ትችላለች:: ቀጣይነት አስተማማኝና ሁሉን አቀፍ የሆነ የእድገታዊ ለውጥ መሰረት ሊጣል ይችላል:: ነገር ግን ይህን ጎጂ ባህል ተቋቁሞ ማለፍና ለቀጣይ ብሄራዊ ለውጥ መስራት ፈታኝ እንደሆነ ግልጽ መሆን አለበት:: ይህን ጎጂ ባህል አጠር አድርጌ ከገለጽኩ በኋላ መፍትሄ ጠቋሚ ሃሳቦች ላይ አተኩራለሁ::

The Addis Paradox and Ethiopia’s Zombie State

  Why can a state that appears stable in its capital simultaneously be losing governing capacity across much of its territory?   This questi...