Saturday 11 February 2023

የመንግስትና የቤተ ክርስቲያን ስምምነት እንዴት?

    ጥር 14 ቀን 2015 ዓ/ም የተካሄደው ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሲመት ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለመንግስትና ለሀገራችን ኢትዮጵያም ከፍተኛ ውጥረትን አስከትሏል። ቤተ ክርስቲያንም ሿሚዎችንም ተሿሚዎችንም አውግዛ ለየቻቸው። መንግስትም በበኩሉ ሕግ የማስከበር ሥራውን እንዲወጣ ቤተ ክርስቲያን አሳሰበች። ይሁንና መንግስት ለሕገ ወጡ ቡድን ሀሳብና ሞራል በመስጠት እንዲሁም ታጣቂዎችን በማሰማራት ሕገ ወጡ ቡድን አብያተ ክርስቲያናትንና መንበረ ጵጵስናዎችን በኃይል እንዲቆጣጠር ማገዙን ቀጠለ። በመሆኑም ጉዳዩ በዋናነት በመንግስትና በቤተ ክርስቲያን መካከል ሆነ። መንግስት ሕግ የማስከበር ግዴታውን እንዲወጣ ቅዱስ ሲኖዶስ ላለፉት ሦስት ሳምንታት ሲወተውት ቆይቷል። የካቲት ሦስት ቀን 2015 ዓ/ም መንግስትና ሲኖዶሱ ለሦስት ሰዓታት የፈጀ ስብሰባ በቤተ መንግስት አካሂደዋል። ይህን ተከትሎ ዛሬ የካቲት አራት ቀን 2015 ዓ/ም ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን አቋም ሙሉ በሙሉ ተቀብሏል። 

Who will Win: Fano or the Government?

  The government's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more   complicated than everyone’s expectation. ...