Saturday 26 January 2019

የተማረ ይግደለኝ! ዩኒቨርስቲዎቻችንን በጨረፍታ


ከሦስት ሳምንታት በፊት ከለውጡ ጋር መደመሬን ለራሴ በራሴ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ሄጄ ነበርበነበሩኝ አራት መናጢ አጫጭር ቀናት ለዓመታት ያላየኋቸውን ቦታዎች ተዘዋውሬ ጎበኘኋቸው። አዲስ አበባ እንደተባለውም ድንገት ከእንቅልፏ ተነስታ ራሷን በመገንባት ላይ ያለች ትመስላለች። ረጃጅም ሕንጻዎች በሁሉም የመዲናይቱ ክፍሎች ተገትረዋል። ገና ያላለቁ ጅምር ሕንጻዎችና በውስጣቸው ምን እንደያዙ የማያሳዩ የታጠሩ ቦታዎችም እንደ ልብ ይታያሉ። እነዚያ የምናውቃቸው ሰፋፊ መንገዶች በባቡሩ መስመር የተነሳ ተለዋውጠዋል። የቆየ ውበታቸው ከስሟል። የባቡሩን ሀዲድ ግራን ቀኝ አቅፈው የያዙ ከፍታ ያላቸው አስቀያሚ ብረቶች የከተማዋን ውበት ለመሻማት ቆርጠው የተነሱ ይመስላሉ።  መንገድ ለማቋረጥም እቅድ ያስፈልጋል። የሆቴሎች፣ የሬስቶራንቶች፣ የካፌዎች፣ የሞቴሎችና የባሮች ብዛት አስገራሚ ነው! የኑሮው ውድነት አይጣል ነው። መሳደብ መሸነፍ ነው! መግደል መሸነፍ ነው! ዘረኝነት መሸነፍ ነው! ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ዐቢይ መሲህ ነው! ወዘተ የሚሉ መፈክሮችን ከታክሲዎችና ከግንቦች ላይ አነበብኩ።

Who will Win: Fano or the Government?

  The government's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more   complicated than everyone’s expectation. ...