Thursday, 26 September 2013

የማታ እንጀራ ይስጥህ!

አገር ቤት ያደገ ወይም የቆየ ሰው ብዙ አባባሎችንና ምርቃኖችን እድሜ ከጠገቡ (እድሜ ካስቆጠሩ) ሰዎች ይሰማል ይማራል:: ከነዚህም ውስጥ የማታ እንጀራ ይስጥህ የሚለው ምርቃት ቀልብን ይስባል:: ገና ነፍስ ሳላውቅ የዚህ አባባል ትርጉም አይገባኝም ነበር:: ትርጉሙን የመጠየቅም እድሉና አቅሙ አልነበረኝም:: ነገር ግን በ20ዎቹ የእድሜየ ክልል ሳለሁ አንድ የተባረከ ሰው ትርጉሙን ሲያብራራ ሰማሁት:: ሳልጠይቅ ያገኘሁት መልስ ነበር:: ከዚያ በኋላ ለአባባሉ ልዩ ክብር መስጠት ጀመርኩ:: 

Friday, 13 September 2013

አዲስ ፕሬዚደንት በአዲስ ዓመት

ሰባት ዓመት ገደማ ነው:: ባህር ዳር ከተማ ፓፒረስ ሆቴል ሻይ ቡና እያልኩ በሆቴሉ የመዋኛ ቦታ ዙሪያ እንደትል የሚርመሰመሱ ህጻናትና አዋቂ ሰዎችን እመለከታለሁ:: በሰዎች ብዛትና በመዋኛ ቦታው ስፋት አለመመጣጠን እየተገረምኩ ሳለ ድንገት የጦር ወሬ የተሰማ ይመስል ህዝቡ ሁሉ መሯሯጥ ጀመረ:: የሆቴሉ ሥራ አሥኪያጅና ሌሎች ሠራተኞች ዋናተኞችንና ሌሎች ተስተናጋጆችን ማዋከብ ጀመሩ:: ሁሉም ሰው ሆቴሉን ባስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ይለማመጣሉም ያመናጭቃሉም::

Friday, 6 September 2013

አዲስ ዓመት አዲስ ስብእና!

ኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ልትቀበል አምስት ቀናት ቀራታል:: 2006 ዓ.ም.:: በዚህ አዲስ ዓመት ሃገራችን ቢያንስ ዳጎስ ያለ ለውጥ ማየት ይኖርባታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ:: ይህ ደግሞ  ምትሃትን ወይም ተአምርን አይፈልግም:: እያንዳንዳችን ድርሻችንን በሚገባ ከተወጣን ሊሳካ የሚችል ግብ ነው:: ከዚህ አኳያ በኔ እምነት ቀጥለው የተዘረዘሩትን ብንወጣ በአዲሱ ዓመት ቢያንስ ትክክለኛውን የለውጥ ጎዳና እንይዛለን:: ይህ ታላቅ ሃገራዊ ጎዳና የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን ቤትና ግቢ ነው:: ይህ እውነታ ተዘንግቶ ለውጥ ለማምጣት መሞከር የራስን ግቢ ሳያጸዱ ያካባቢን ንጽህና እጠብቃለሁ ብሎ  እንደማሰብ ነው::

Tuesday, 3 September 2013

የትግራይ ህዝብ ሥጋትና የህወሓት ፖለቲካ

የትግራይ ህዝብ ከኢሕአዴግ መንግስት ምን ተጠቅሟል? የትግራይ ህዝብና መንግስት ምን አይነት ግንኙነት አላቸው? እነዚህንና ተያያዥ ጥያቄዎችን በተመለከተ አብርሃ በላይ ከመቀሌ አጥጋቢ መልስ ሰጥቷል:: አብርሃ እንደመነሻ ያደረገው ከአንድ የትግራይ ተወላጅ የቀረበለትን ጥያቄ ነው::  ጥያቄውም ይህ ነው:: “ኢህኣዴግን ትቃወማለህ፣ ግን ህዝብን ለለውጥ ኣነሳስተህ ከህወሓት የባሱ ፅንፈኛ የፖለቲካ ድርጅቶች ስልጣን ቢይዙስ ??? ስትቃወም ስለዉጤቱም ማሰብ ኣለብህ። በምትፅፋቸውን ነገሮች ለአዳንድ የትግራይ ጠላቶች መጋበርያ እየሆንክ ነው።”

Who will Win the War: Fano or the Government?

  As a Prelude The federal government of Ethiopia's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more  complic...